





ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም አሶሳ፤
የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ሐጂ ባበክር ኸሊፋ በሆሞሻ ወረዳ የፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ እርሻ ጎበኙ፤
በፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ እርሻ ልማት ድርጅት በአንድ አመት ተኩል ጊዜ የተተከሉ የብርቱኳን፣ የሎሚ፣ የሙዝና የሮማን ፍራፍሬ ችግኞች ለገበያ እየቀረበ መሆኑን አቶ ፍቃዱ ነመራ የድርጅቱ ባለቤት ተናግረዋል፤
የክልሉ መንግስት በሰጠው የግብርና ኢንቨስትመንት በአትክልትና ፍራፍሬ እና በእንስሳት ልማት በአጭር ጊዜ ውጤታማ መሆኑን አቶ ፍቃዱ ነመራ ተናግረዋል፤
በተጨማሪ እሸት በቆሎ፣ አንጮቴ፣ ቆጮ፣ ድንችና ካዛባ ከበጋ እስከ ክረምት ለገበያ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል፤
የግብርና ቢሮ ኃላፊ ክቡር ሐጂ ባበክር ኸሊፋ ችግኝ በመትከል በረከትን መቀበልና ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሆነ ተናግረዋል::
Categories:
